ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ.ር) በፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ።

34

ባሕር ዳር: ግንቦት 12/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ.ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ በደረሰው አሰቃቂ የሄሊኮፕተር አደጋ ሕይወታቸውን ላጡት የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር አብዱላሂይን በኢትዮጵያ ሕዝብ፣ መንግሥትና በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡

ለፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲና አሚር አብዱላሂይን ቤተሰቦች እንዲሁም ለኢራን ሕዝብና መንግሥትም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየኢትዮጵያ አየር መንገድ 1 ሺህ 445ኛውን የሐጅ ጉዞ ለማካሄድ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ።
Next article“የኮሙኒኬሽን እና የሬዲዮ ሲግናልን በአግባቡ ማሥተዳደር የዲጅታል ሥነምህዳሩን ከማስተካከል ባለፈ ሀብትን በአግባቡ እና በፍትሐዊነት የመጠቀም ጉዳይ ነው” በለጠ ሞላ (ዶ.ር)