ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ከቢግ ዊን ፊላንትሮፒ መሥራች እና ፕሬዝዳንት ጄሚ ኩፐር እና ቡድናቸው ጋር ተወያዩ።

40

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 5/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ዛሬ ከቢግ ዊን ፊላንትሮፒ መሥራች እና ፕሬዝዳንት ጄሚ ኩፐር እና ቡድናቸው ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል። ድርጅቱ በሀገራችን በግብርና፣ በትምህርት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ድህነት ቅነሳ ዘርፎች አበረታች ሥራዎች ሰርቷል ብለዋል።

ቢግ ዊን በሰቆጣ ቃል ኪዳን አተገባበር እና ከመንግሥት ጋር በሚሠሩ በሌሎች የልማት ሥራዎች ዙሪያ ምክክር አድርገናል፡፡ ይህን የትብብር ምዕራፍ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ በጀመርናቸው እና በሌሎች አዳዲስ ዘርፎች በትብብር ለመስራት ተስማምተናል ነው ያሉት።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በከተማ አሥተዳደሩ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያስችል ሥርዓት እየተዘረጋ ነው” ጎሹ እንዳላማው
Next articleርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የባሕር ዳር ዓባይ ድልድይ ምረቃ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር