ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ገቢ ማሰባሰቢያ የአንድ ጀንበር እንቅስቃሴን ተቀላቅለዋል።

44

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 4/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በዚህም ለአንድ ጀንበር የገቢ ማሰባሰብ ላይ የተቀላቀሉ የታክሲ ማኅበር አባላትን አበረታትተዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ (ዶ.ር) ባስተላለፉት መልዕክት በየመንገዱ የመጸዳዳት ጎጂ ልማድን መኮነን ብቻ ሳይኾን በመንገዶች፣ በምግብ ቤቶች፣ በሆቴሎች እና ቢሮዎች መጸዳጃ ቤቶች የመገንባትን አስፈላጊነትት ተናግረዋል።

ይህንን የጽዳት ሥራ በትብብር እንሠራለን ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ የአዲስ አበባ ታክሲ ማኅበራት ሕግ አክብሮ በመሥራት ያላቸውን ጥሩ ምግባር ለመጸዳጃ ቤት ግንባታ እና ለአካባቢ ጽዳት ለሚኖራቸው አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና ከፍተኛ መሪዎች በጽዱ ኢትዮጵያ ቴሌቶን ላይ በጋራ ተሳተፉ።
Next articleየፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር የጽዱ-ኢትዮጵያ ንቅናቄን በድጋሜ ተቀላቀሉ።