“የዓባይ ድልድይ ኅብረታዊ ምሉዕነትን ለማፅናት ከክልላዊ ወሰኖች የሚሻገር ትርክት የመቅረፅ ትልማ ማሳያ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

51

ባሕር ዳር: ግንቦት 04/2016 ዓ.ም (አሚኮ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) እንደገለጹት ዛሬ በባሕርዳር ከተማ የተመረቀው የዓባይ ድልድይ በሰዎች መካከል ያለን ግንኙነት በማጠናከር እና የንግድ እድሎችን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ርምጃ ነው። ከግዘፋዊ ቁሳዊ መዋቀሩ ባሻገርም ልዩነቶችን የማጥበብ፤ በተቃራኒ ጎራ ላሉ ሰዎች መገናኛ ድልድዮችን የማነፅ ርዕያችን መዘርጊያ ምልክት ነው ብለዋል።

ኅብረታዊ ምሉዕነትን ለማፅናት ከክልላዊ ወሰኖች የሚሻገር ትርክት የመቅረፅ ትልማ ማሳያ ነው ብለዋል። ግባችን በክልከላ እና ቁንፅልነት የሚመሩ የአእምሮ ውቅሮች እና ትርክቶችን በማስወገድ በሁሉም ዘንድ ትብብርን እና አንድነት ማሳደግ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአቶ ያደታ ጁኔዲ ለ#ጽዱኢትዮጵያ ዲጂታል ቴሌቶን የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ።
Next article“ግባችን በሁሉም ዘንድ ትብብርን እና አንድነት ማሳደግ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)