“የ50 ሚሊየን ብር ዕቅድን በማለፍ 120 ሚሊየን መግባት አለብን” የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጀማል አህመድ

25

ባሕር ዳር: ግንቦት 4/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ለጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት 64 ሚሊየን ብር ደግፏል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጀማል አህመድ የድርጅቱ ሠራተኞች 13 ሚሊየን፣ ድርጅቱ 50 ሚሊየን እንዲኹም እሳቸው በግላቸው አንድ ሚሊዮን ብር በድምሩ 63 ሚሊየን ብር ለጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት መደገፋቸውን ገልጸዋል።

ሁኔታውን እያየን ድጋፋችን እንቀጥላለን ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው የንቅናቄውን የ50 ሚሊየን ዕቅድ ማለፍ እና 120 ሚሊየን መግባት አለብን ብለዋል። አቶ ጀማል ንቅናቄው ስብራታችንን ከሚጠግኑ ፕሮጀክቶች አንዱ ነው ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የጎርጎራ ሎጅ ፕሮጀክት እና አዲሱ የዓባይ ድልድይ ዓባይ እና ጣናን አዛምደዋቸዋል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ
Next article“ የባሕርዳር ውበት፤ የግዮን ሰገነት”