ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ለጽዱ ኢትዮጵያ የአንድ ጀንበር 50 ሚሊየን ብር የማሠባሠብ የዲጂታል ቴሌቶን ዛሬ አስጀምረዋል።

39

ባሕር ዳር: ግንቦት 4/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ሚያዝያ 18/ 2016 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የ“ጽዱ ጎዳና – ኑሮ በጤና” ንቅናቄ ጽዱ እና ውብ ሀገርን የመፍጠር ዓለማ አለው።

ፕሮጀክቱ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበር ሲኾን በፕሮጀክቱ፦

👉 የመጸዳጃ ቦታዎች ይገነባሉ።
👉 የመፋሰሻ ቦዮች ተጠርገው ይከፈታሉ።
👉 በመኖሪያ እና መሥሪያ ቤቶች አካባቢ ያሉ ቦታዎች ይጸዳሉ፣ ይለማሉ።
👉 የአመለካከት ለውጥ እንዲኖር የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ይሠራል።
👉 የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
👉 ጽዱ እና ውብ ሀገር በመፍጠር የገጽታ ግንባታ ይፈጥራል።

ለጽዱ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 50 ሚሊየን ብር የገቢ ማሰባሰቢያ (ዲጂታል ቴሌቶን) ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያበረክቱ ጥሪ ቀርቦል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከሩሲያ ለኢትዮጵያ የተሰጠ ተቋም
Next articleበ1 ሰዓት ውስጥ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ።