“በግብርና ዘርፍ ያገኘነውን ስኬት በኢንደስትሪው ዘርፍ ለመድገም ትልቅ ትልም አለን” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

37

ባሕር ዳር: ግንቦት 1/2016 ዓ.ም (አሚኮ)የገዳ ኢንዱስትሪ ዞን ምሥረታ ዛሬ ተካሂዷል። በምሥረታው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) “በግብርና ዘርፍ ያገኘነውን ስኬት በኢንደስትሪው ዘርፍ ለመድገም ትልቅ ትልም አለን” ብለዋል። የገዳ ኢንደስትሪ ዞን የሀገሪቱን እና የቀጣናውንን አቅም በመግለጥ ይህን ርዕያችንን ለማሳካት የሚረዳ ቁልፍ ተቋም ኾኖ ያገለግላል ብለዋል።

የሉሜ ነጻ የንግድ ቀጣና በኢንደስትሪ ዞን ውስጥ ኾኖ በምሥረታው ብሎም ተግባራዊ ሥራ በሚጀምርበት ወቅት ከድሬዳዋ በመቀጠል ሁለተኛው ነጻ የንግድ ቀጣና የሚሆን ሲኾን ይህም ለኢኮኖሚ እድገት እና ልማት ያሉ እድሎችን ያሰፋል ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ከ21 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለእርሻ መዘጋጀቱ ተገለጸ።
Next articleለአማራ ክልል ቴክኖሎጂን የሚያዘምኑ ቁሶችን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ አደረገ፡፡