የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን በመቀላቀል የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።

21

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን በመቀላቀል የ5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል። ኮርፖሬሽኑ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ይፋ የሆነውን የ“ጽዱ ጎዳና – ኑሮ በጤና” ንቅናቄን በመደገፍ ነው አስተዋጽኦ ያደረገው።

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ውብና ዘመናዊ ከተማ ለመፍጠር የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት የሚያግዙ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ መኾኑንም አስታውቋል። የሚገነባቸው ዘመናዊ ሕንጻዎችና የመኖሪያ መንደሮች ውበትን፣ ጥራትንና ዘመናዊነትን ታሳቢ ያደረጉ እንዲኾኑ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ የገለጸው ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ ለጽዱ ኢትዮጵያ ንቅንናቄ መሰል ድጋፎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አመላክቷል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleናሚቢያ ኤች.አይ.ቪ እና የጉበት ቫይረስ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ ለማድረግ እየሠራች ያለችው ሥራ ከአፍሪካ ቀዳሚ እንዳደረጋት የዓለም ጤና ድርጅት ገለጸ።
Next articleየጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ አካል የኾነው የጽዳት እና አረንጓዴ ልማት ሥራ ተጀመረ፡፡