ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ነቀምቴ ከተማ ገቡ።

107

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በምሥራቅ ወለጋ ዞን በተዘጋጀው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ለመገኘት ነቀምቴ ከተማ ገብተዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎችም በድጋፍ ሰልፍ ላይ ለመታደም ነቀምቴ ከተማ ገብተዋል፡፡

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎቹ አዲስ ከተገነባው የነቀምት አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ከኢትዮጵያ ለዓለም የሥራ ገበያ የሚቀርበው የሰው ኀይል ሥልጠና የመዳረሻ ሀገራትን ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ ሊኾን ይገባል” የዓለም ባንክ
Next article“በተሠራው ቅንጅታዊ ሕግ የማስከበር ሥራ በዞኑ አንጻራዊ ሰላም እየታየ ነው” የምሥራቅ ጎጃም ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ ዋለ አባተ