
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በጫካ ፕሮጀክት ሠራተኞች መካከል ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ እንደሚያመለክተው ዶክተር ዐቢይ በጫካ ፕሮጀክት ላይ እየሠሩ ላሉ ሠራተኞችን፣ ለበዓል በተዘጋጀ የምሳ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ነው የእንኳን አደረሳችሁ መልክት ያስተላለፉት::
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!