የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ-ግብረ ኃይል የትንሣዔ በዓል በሰላም እንዲከበር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ።

24

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 25/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ሕዝበ ክርስቲያኑ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣዔ በዓል በሰላም እንዲያከብር ዝግጅት ማጠናቀቁን የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ-ግብረ ኃይል አስታወቀ። በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አሥተዳደሮች ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ወደ ተግባር መግባቱን የጋራ ግብረ-ኃይሉ አስታውቋል፡፡

ሕዝቡም የአካባቢውን ሰላም እና ደኅንነት የሚያውኩ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ከጋራ ግብረ-ኃይሉ ጎን እንዲቆም ጠይቋል፡፡ ግብረ-ኃይሉ ለመላው የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleማኅበረሰቡ በዓልን ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ አደጋዎችና ወንጀሎች እንዲጠነቀቅ የደብረ ብርሃን ከተማ ፖሊስ መምሪያ አሳሰበ።
Next articleድምጽ አልባው ገዳይ በሽታ!