
ባሕር ዳር: ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ኀላፊ አደም ፋራህ የልማት ሥራዎችን ለመመልከት ባሕር ዳር ከተማ ገብተዋል።
ከፍተኛ መሪዎቹ በባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ ሌሎችም የክልሉ ከፍተኛ መሪዎች እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል። በቆይታቸው በወቅታዊ የፀጥታ እና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ እንደሚዎያዩ ይጠበቃል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!