የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ኾነ።

44

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 21/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ኾኗል።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሐምሌ 3-5 ለማኅበራዊ ሳይንስ ሐምሌ 9-11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።

በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 30-ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ሐምሌ 6-7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይኾናል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleትኩረት ሰጥቶ ግብዓት እያሟላ መኾኑን የሰሜን ወሎ ዞን ገለጸ።
Next article195 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት መቻሉን የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ፡፡