በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመራ ልዑክ ኬንያ ገባ።

81

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 21/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው በዓለም አቀፉ የልማት ማኅበር (አይ ዲ ኤ) 21ኛ የማሟያ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ናይሮቢ ኬንያ ገብተዋል።

ጉባዔው ማኅበሩ፣ ደጋፊዎች እና ተባባሪ አካላት በአፍሪካ የልማት የገንዘብ ድጋፍ ቀዳሚ የትኩረት መስኮችን ለማመላከት እና አፅንዖት ለመስጠት ያለመ ነው ተብሏል።

የገንዘብ ድጋፍ አቅራቢዎች በ21ኛው የማኅበሩ ዘመን ድጋፋቸውን ለመጨመር በጽኑ እንዲያጤኑ የማሳሰብ ዓላማ ያነገበም ነው።

ድጋፉ የአፍሪካን የልማት ተግዳሮቶች እና መልካም እድሎች በተገቢው መንገድ ለማስተናገድ አስፈላጊ ነው ተብሏል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበትምህርት ለትውልድ ሕዝባዊ ንቅናቄ ከ25 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሃብት ማሰባሰብ መቻሉ ተገለጸ፡፡
Next articleኢ-ኮሜርስ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡