
ደሴ: ሚያዚያ 20/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመራ የከፍተኛ መሪዎች ልዑክ ቡድን የልማት ሥራዎችን ለመመልከት ደሴ ገባ። መሪዎች የወሎ መናገሻ፣ የፍቅር፣ የመቻቻልና የአንድነት ተምሳሌት ወደ ኾነችዉ ደሴ ከተማ ሲደርሱ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና የሥራ ኀላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገዉላቸዋል።
ልዑካን ቡድኑ በሚኖረዉ ቆይታ በተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በከተማዋ የተሠሩ ትልልቅ የልማት ተግባራትን ተመልክተው ለተጨማሪ ልማት ግብዓት የሚኾኑ ውይይቶችንም እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!