የሲዳማ ሕዝብ ዘመን መለወጫ በአል “ፊቼ ጫምባላላ” በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው።

43

አዲስ አበባ፡ ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም (አሚኮ) “ሁላችንም የምንኮራበት የጋራ ቅርሳችን እና እሴታችን ነው!” በሚል መሪ መልእክት የፊቼ ጫምባላላ በዓል በአዲስ አበባ በወዳጅነት አደባባይ እየተከበረ ይገኛል።

ፊቼ ጫምባላላ ከ9 ዓመታት በፊት የዓለም ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ የሚታወስ ነው። የፊቼ ጫምባላላ በአል ተምሳሌትነቱ ዕርቅና ይቅርታ፣ ሰላምና ፍቅር እንዲሁም አንድነትና መከባበር ነው።

በበዓሉ የክብር እንግዳ ሆነው ከተገኙ መካካል የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋ (ዶ.ር) ለኢትዮጵያም ሆነ ለዓለም በርካታ ጠቃሚ እሴቶች ያሉትን ይህንን በዓል መጠበቅና መንከባከብ ይገባል ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሀገራት ግጭቶችን በምክክር የፈቱበትን ልምድ እኛም ተግባራዊ ማድረግ አለብን” ፕሬዝዳንት ሳኅለ ወርቅ ዘውዴ
Next article“ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ከስምንት ሚሊዮን በላይ ለሚኾኑ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ እየሠራን ነው” የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን