የጎጃም ኮማንድፖስት መረጃ ባደረገው ክትትል ለጽንፈኛው ቡድን ሊደርስ የነበረ 2 ሺ 500 ጥይት በቁጥጥር ስር አዋለ።

20

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 15/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በባሕር ዳር ከተማ ቀበሌ 13 በተደረገው የክትትል ኦፕሬሽን ከተያዘው 2 ሺ 500 የኤ ኬ ኤም ጥይት በተጨማሪ ዘጠኝ ካዝና፣ የመሣሪያ መጠገኛ እና ሌሎች መሰል ቁሳቁሶች ለጽንፈኛው ሲጓጓዙ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የጎጃም ኮማንድፖስት መረጃ ከዚህ ቀደምም የሕብረተሰቡን ሰላም ለማናጋት ሲጓጓዙ የነበሩ 5 ሺ ጥይት፣ 32 ቦምብ እና ሌሎች ለሽብር ሥራ የሚውሉ ቁሳቁሶች ለጽንፈኛው ቡድን ከመድረሳቸው በፊት የማክሸፍ ግዳጆችን ሲወጣ ቆይቷል።

ጽንፈኛው ቡድን በከተማ የሽብር ሥራዎችን ለመፈጸም ቦምቦችን እና ጥይቶችን ከያለበት እያፈላለገ እንደሚገኝ ስለታወቀ ይህንን የሚያመክን የክትትል እና የአሰሳ ግዳጆች ወደፊትም አጠናክሮ በመቀጠል የሕዝብ ደኅንነት የመጠበቅ ተልዕኮው ይቀጥላል ሲል የጎጃም ኮማንድፖስት አሳውቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየግብርና ባሕል እየኾነ የመጣው የበጋ መስኖ ልማት!
Next articleበጀልባ መገልበጥ አደጋ የ16 ኢትዮጵያውያን ሕይዎት አለፈ፡፡