ቀጣናዊ ችግሮች እንዲፈቱ ኢትዮጵያ ከወዳጅ ሀገራት እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እንደምትሠራ ተገለጸ።

22

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን እና ፍላጎቷን መሰረት ያደረገ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ታራምዳለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምሥራቅ ጋር ካላት መልክዓ ምድራዊና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር አኳያ የቀጣናው ቀውስ ቀጥተኛ ተፅእኖ እንደሚያሳድርባት ተናግረዋል። በመኾኑም ችግሮች እንዲፈቱ ከወዳጅ ሀገራት እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በትብብር እንደምትሠራ ገለጸዋል።
በሰላም ዕጦት ውስጥ ያሉ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሰላም እንዲረጋገጥም አበክራ እንደምትሠራም ተገልጾል።

ኢዜአ እንደዘገበው በጎረቤት ሀገራት ሰላም እና መረጋጋት እንዲፈጠር በታሪክ የነበራትን የሰላም ማስከበር ሚና አጠናክራ እንደምትቀጥልም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየምሥራቅ ጎጃም ዞን ኮማንድፖስት ባከናወነው ጠንካራ ሥራ በአካባቢዉ ሰላም መሥፈኑን የደጀን ወረዳ አሥተዳደር ገለጸ።
Next articleምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ስታርት አፕ ኢትዮጵያ አውደ ርእይን ጎበኙ።