“ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እንደ ሀገር ለጀመርነው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ ፋይዳው የጎላ ነው” አቶ ተመሥገን ጥሩነህ

63

ባሕር ዳር: ሚያዝያ 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እንደ ሀገር ለጀመርነው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ በዛሬው ዕለት የፕሮግራሙ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ገምግመንም ገልጸዋል፡፡

በቀሪ ወራት መፈጸም ያለባቸው ተግባራትን ተለይተዋል ነው ያሉት። በዚህ መሰረት በዓመቱ ለማሳካት የታቀዱ ተግባራትን በተሟላ መልኩ ለመፈጸም ከፕሮግራም ጽሕፈት ቤቱ እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ሚንስትሮች እና የተቋማት ኀላፊዎች ጋር የጋራ መግባባት መፈጠሩን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አሳውቀዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleትምህርት አቋርጠው የቆዩ ትምህርት ቤቶች ወደ ማስተማር ሥራ መመለሳቸውን የምሥራቅ ጎጃም ዞን አስታወቀ፡፡
Next articleየብረት ምርትን ማሳደግ የሀገሪቷ የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ አካል መኾኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ተናገሩ።