
ባሕር ዳር: ሚያዚያ 7/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ለሁለት ቀናት የሚቆየው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በአዲስ አበባ ተጀምሯል።
በጉባኤው ከተለያዩ ሀገራት የመጡ የሃይማኖት አባቶች፣ የተለያዩ አደረጃጀቶች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ እና የዘርፉ ተመራማሪዎች እየተሳተፉ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ዛሬ እና ነገ በሚካሄደው በዚህ ጉባዔ ላይ ከ37 የሚበልጡ ሀገራት እየተሳተፉ እንደሚገኝም ኢቢሲ ዘግቧል።
ጉባኤው በዓለም አቀፍ ደረጃ ሁለንተናዊ ትብብርን በሚያጠናክር እና በሰላም ግንባታ እንዲሁም በዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ጉዳይች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!