“ዒድ ማለት መደሰት ማለት ነው፤ ዒድ ማለት የአንድነት፣ የአብሮነት፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ በዓል ማላት ነው” ሼህ መሐመድ አደም

66

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 2/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በሰቆጣ ከተማ የ1 ሺህ 445ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል እየተከበረ ነው፡፡የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዋና አሥተዳዳሪ ኃይሉ ግርማይ በሰቆጣ ከተማ አንዋር መስጂድ ተገኝተው እንኳን ለ1 ሺህ 445ኛው ዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋ።

በዓሉ የሰላም፣ የወንድማማችነት፣ የእህታማማችነት፣ የደመቀ አንድነት የምናዳብርበት እና የፍቅር እንዲኾንላችሁ እመኛለሁ ሲሉ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

የአንዋር መስጊድ ኢማም ሼህ መሐመድ አደም በበኩላቸው “ዒድ ማለት መደሰት ማለት ነው፤ ዒድ ማለት የአንድነት፣ የአብሮነት፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ በዓል ማላት ነው” ብለዋል፡፡

መረጃው፡- የዋግ ኽምራ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“እስላም ሰላም ነው፤ ለሰላም አብረን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሠራለን” ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው
Next article1 ሺህ 445ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰሜን ወሎ ዞን አላማጣ ከተማ እየተከበረ ነው።