“በረመዷን ወር ሲፈጸሙ የቆዩትን የመተሳሰብ እና የመረዳዳት በጎ ተግባር ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ማድረግ ይገባል” አቶ ይርጋ ሲሳይ

44

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 445ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ ብለዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በመቻቻል አብሮ የመኖር እሴት እንዲጎለብት፣ የመተባበር፣ የመደጋገፍ እና እርስ በእርስ የመከባበር መልካም ተግባር የበለጠ እንዲጎለብት ማድረግ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት፡፡

አቶ ይርጋ ሲሳይ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰፈሩት በተለይም በረመዷን ወር ሲፈጸሙ የቆዩትን የመተሳሰብ እና የመረዳዳት በጎ ተግባር ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ማድረግ እንደሚጠበቅም አብራርተዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የዒድ አል ፈጥር በዓል ሲከበር ለአንድነት እና ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት መኾን አለበት” አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
Next articleበጥቂት ጽንፈኛ ኃይሎች አስተሳሰብ እና እኩይ ድርጊት የሚበተን ሀገር እና ሕዝብ እንደማይኖር የምድረ ገነት ከተማ አሥተዳደር ነዋሪዎች ገለጹ፡፡