ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለዒድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡

83

ባሕር ዳር: ሚያዚያ 1/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እንኳን ለ1ሺህ 445ኛው ዓመተ ሂጅራ ዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ብለዋል።

ርእሰ መሥተዳድሩ ሕዝበ ሙስሊሙ በተባረከው የረመዷን ወር እርስ በእርስ በመደጋገፍ እና በመረዳዳት እንዳሳለፈው ሁሉ ታላቁን የዒድ አልፈጥር በዓልን ሲያከበርም መልካምነት እና ደግነትን የበለጠ የሚያጸናበት፤ ለሰላም እና ለልማት በአንድነት ለመትጋት ትብብር እና ቅንጅት የሚጠናከርበት በዓል ይኾን ዘንድ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ለዒድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።
Next article“ሰራዊቱ የሕዝቡን ሰላም ለማምጣት እና ሕግ ለማስከበር ባደረገው ስምሪት ጽንፈኛው ቡድን ቆሞ የመዋጋት ቁመናውን አጥቷል” ጀኔራል አበባው ታደሰ