ክልሉን በውክልና ጦርነት ማፍረስ አይቻልም ሲሉ በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ የሳልመኔ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

44

ባሕር ዳር: መጋቢት 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ ሳልመኔ ከተማ ሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።,ሠልፈኞቹ ባሰሙት መልእክት እንዳሉት ኢትዮጵያ የዓድዋ ድልን ዳግም እያደሰች የምትገኝበት ጊዜ ላይ እንደኾነች ተናግረዋል፡፡

የላቀ ሕዝባዊ ተሳትፎ ለኢትዮጵያዊያን ብልጽግና ወሳኝ እንደኾ ያስረዱት ሠልፈኞቹ በክልሉ ያለውን አንጻራዊ ሰላም በአጭር ጊዜ ወደ ዘላቂ ሰላም ለማሽጋገር ከለውጡ አመራር ጋር በጋራ እንደሚሠሩ ነው ያብራሩት፡፡ ሀገራዊ ለውጡ ኢትዮጵያውያንን የታደገ እና ህልውናን ማስቀጠል ያስቻለ እንደኾነም አስገንዝበዋል፡፡

እንደ አልብኮ ወረዳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት መረጃ ክልሉን በውክልና ጦርነት ማፍረስ አይቻልም የሚሉ እና ሌሎች መልዕክቶችም በሠልፈኞቹ ተስተጋብተዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በደቡብ ጎንደር ዞን በላይ ጋይንት ወረዳ እና ነፋስ መውጫ ከተማ ተካሂዷል፡፡
Next articleበአቀስታ ከተማ ሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡