
ባሕር ዳር: መጋቢት 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሚ ሩዋንዳ ችግር ገጥሟት በነበረበት ወቅት ኢትዮጵያ ያደረገችውን ድጋፍ አስታውሰው አመስግነዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በወጣትነት ዘመናቸው ሰላም አስከባሪ በመኾን ጭምር ሀገሪቱን ከችግር ለመታደግ ያደረጉትን እገዛም አውስተዋል፡፡ “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ሩዋንዳን ከችግር ለመታደግ አግዘዋል” ሲሉ ነው የገለጹት ፖል ካጋሚ።
የሩዋንዳውያን የ”ኪዊቡካ 30″ ዓመት መታሰቢያ መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡ መርሐ ግብሩ በሩዋንዳ የተፈጸመውን የዘር ጭፍጨፋ 30ኛ ዓመት የሚያስብ ነው፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!