የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

17

ባሕር ዳር፡ መጋቢት 26/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በጉባኤው የከተማዋን የመልካም አሥተዳደር ሥርዓት ለማሻሻል፣ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ፣ ካለፉት ወራት አፈጻጸም በመነሳት እንደሚገመግም እና የቀጣይ ጊዜ የትኩረት አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል።

ምክር ቤቱ የከተማ አሥተዳደሩን የ6 ወር ሥራ አፈጻጸም፣ የደንብ ማስከበር መምሪያ፣ የኦዲት ሪፖርት እና የባሕር ዳር ስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ማቋቋሚያ ደንብ ገምግሞ እንደሚያጸድቅም ይጠበቃል።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው የከተማ አሥተዳደሩን የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በማቅረብ ላይ ናቸው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ እና አፋር ክልሎችን በማገናኘት ትልቅ ፋይዳ ያለው የሐይቅ – ቢስቲማ – ጭፍራ የመንገድ ፕሮጀክት ሥራ ከ29 በመቶ በላይ ደረሰ።
Next articleየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 20ኛ መደበኛ ስብሰባ የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅን መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ፡፡