በደቡብ ጎንደር ዞን በስማዳ ወረዳ የማዳበሪያ ስርጭት እየተካሄደ ነው፡፡

29

ባሕር ዳር: መጋቢት 23/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ጎንደር ዞን በስማዳ ወረዳ የማዳበሪያ ስርጭት እየተካሄደ መኾኑን የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡ ለ2016/17 የምርት ዘመን ከ60 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በሰብል የሚሸፈን መኾኑንና ለዚህ ደግሞ 80 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማስገባት እየሠራ እንደሚገኝም ተገልጿል።

ለአርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ ማሰራጫ ኩፖን በማዘጋጀት በ1ኛ እና 2ኛ ዙር የገባውን ማዳበሪያ ቅድሚያ ወደ ዘር ለሚገቡ ደጋማ ቀበሌዎች እየተሰራጨ ነው ብሏል ጽሕፈት ቤቱ። በእቅድ የተያዘውን የአፈር ማዳበሪያ ሙሉ በሙሉ ወደ ወረዳው ለማስገባት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሠራ መኾኑን ከወረዳው መንግሥት ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአማኞች የቤተክርስቲያኒቷ “መንፈሳዊ ትጥቆች” ተደርገው የሚወሰዱትን ጾም፣ ጸሎት እና ምጽዋት ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው የሃይማኖት አባቶች ተናገሩ፡፡
Next articleየታችኛው ርብ መስኖ እና ድሬይኔጅ ፕሮጀክትን ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡