
“ዛሬ በምዕራብ ኦሞ ዞን በመጎብኘቴ ደስታ ተሰምቶኛል። የተፈጥሮ ውበት እና እምቅ ሃብት ሞልቶ የፈሰሰበት፤ በትክክለኛ የልማት ድጋፍ እና የሰላም ከባቢ ሁኔታ ለኢትዮጵያ ሀገራችን የእድገት ርምጃ በእጅጉ አስተዋፅዖ የሚያደርግ አካባቢ ነው።
ምንም እንኳ ሁሉንም የልማት ፍላጎት ማሟላት ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ለሆነ የልማት መፍትሔ መሠረት ለመጣል በፅናት መቆሟን ለአካባቢው ሕዝብ አረጋግጫለሁ።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)