
ባሕር ዳር: መጋቢት 9/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ኡስማን ዲዮን ጋር መወያየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ኡስማን ዲዮን ጋር ተወያይተዋል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ላደረገው ያላሳለሰ ድጋፍ እናመሰግናለን” ብለዋል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!