እንደ ሀገር መግባባት ላይ ባልተደረሰባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማድረግ በመተማመን ላይ የተመሠረተ የፖለቲካ ሥርዓት ለመገንባት እየሠራ መኾኑን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ

49

አዲስ አበባ: መጋቢት 7/2016 ዓ.ም (አሚኮ)እንደ ሀገር መግባባት ላይ ባልተዳረሰባቸው መሠረታዊ ጉዳዩች ላይ ምክክር በማድረግ በመንግሥት እና በሕዝብ መካከል መተማመን ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሥርዓት ለመገንባት እየሠራ መኾኑን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል። ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እና ለመጪው ትውልድ ጠንካራ መሠረት ያለው ሀገር ለማስረከብ በጋራ መሥራት እንደሚገባ ተገልጿል።

ኮሚሽኑ የአጀንዳ አሠባሠብ፣ ምክክር እና ለሀገራዊ ጉባኤ የተወካዮች የልየታ አሠራር ሥርዓትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እና የግብዓት ማሠባሠቢያ መድረክ እያካሄደ ነው።

የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመክፈቻ ንግግራቸው ምክክሩ አሳታፊ፣ ግልጽ እና ኅብረተሰቡ የኮሚሽኑን ተግባር እና ኀላፊነት እንዲያውቅ ከቅድመ ዝግጅት ሥራው ጀምሮ መሥራታቸውን ገልጸዋል።
ችግሮችን ለመፍታት ምክክርን ብቻ አማራጭ ማድረግ እንደሚገባም አንስተዋል።

ኢትዮጵያን የሚመስል አካታች ብዝኃነትን የሚያሳይ ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግ ሁሉም ኀላፊነቱን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል።

ዘጋቢ፦ ቤተልሄም ሰለሞን

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየውይይት መድረኮቹ ሕዝቡ ለሀገረ መንግሥቱ ቀጣይነት ያለውን ዝግጁነት እና ቁርጠኛ አቋም ያንጸባረቀባቸው መኾናቸውን ለገሰ ቱሉ (ዶ.ር) ገለጹ።
Next articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኢትዮጰያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና ከአባል አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች ጋር ተወያዩ።