
ወልድያ: መጋቢት 06/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በመኖሪያ ቤት ግቢና በመንግሥታዊ ተቋማት የከተማ ግብርናን እያስፋፋ መኾኑን የከተማ አሥተዳደሩ ግብርና መምሪያ ኀላፊ ደስታ ሰጠ ገልጸዋል።
በያዝነው ዓመት እስካሁን እያለሙ ካሉት ነዋሪዎች በተጨማሪ ከ2 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን ተደራሽ የሚያደርግ የዘርና የፍል አቅርቦት መዘጋጀቱን ነው የገለጹት።
መምሪያው ከዘርና ፍል አቅርቦት በተጨማሪ ለጓሮ አትክልት አልሚ የከተማ ነዋሪዎች የግብርና ባለሙያዎቹ የአትክልት እንክብካቤ እና ክትትል ላይ ትኩረት ያደረገ ድጋፍ እያደረጉ መኾኑን ነግረውናል።
የጓሮ አትክልት በማልማት እየተጠቀሙ ያሉ ነዋሪዎች በበኩላቸው አትክልት ጋር መዋል፣ አትክልትን መንከባከብ ተዝናኖትን ይፈጥራል ነው ያሉት። ከተዝናኖት ባለፈም የተመጣጠነ ምግብ ለመመገብ መቻላቸውንም አስገንዝበዋል። አሁን ላይ በጓሯቸው ቀይ ስር፣ ሰላጣ፣ ቆስጣ፣ ድንች፣ ካሮት፣ ጎመንና መሰል የጓሮ አትክልቶችን እያለሙም ይገኛሉ፡፡ በጓሯቸው አትክልትን ማልማታቸው ወጫቸውን መቀነስ እንዳስቻላቸው ነው የተናገሩት።
ዘጋቢ፡- ካሳሁን ኃይለሚካኤል
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!