የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአቶ ክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብት አነሳ።

30

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 16ኛ መደበኛ ጉባዔው የአቶ ክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብት አንስቷል።

የፍትሕ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ የምክር ቤት አባሉን ያለመከሰስ መብት መነሳት አስመልክቶ ለሕዝብ ተወካዮች ማብራሪያ አቅርበዋል።

በማብራሪያቸውም፤ አቶ ክርስቲያን በአማራ ክልል ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር አብረው ሲሠሩ እንደነበር የፌዴራል ፖሊስ መርምሮ ለአቃቢ ሕግ ልኳል ብለዋል።

ምክር ቤቱም በውሳኔ ቁጥር 9/16 የአቶ ክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብት አንስቷል።

Previous articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ‘ለነገዋ’ ማዕከልን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።
Next articleሴቶችን ማሰብ፣ ማነጽ፣ ማስተማር፣ እድል መስጠት ካልቻልን እንደ ሀገር ለመለወጥ ያለን ሕልም ሙሉ አይኾንም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)