ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ‘ለነገዋ’ ማዕከልን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ።

28

ባሕር ዳር: መጋቢት 05/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዛሬ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶችን ለሚጋፈጡ ሴቶች መደገፊያ እንዲሆን የተቋቋመውን ‘ለነገዋ’ ማዕከልን መርቀው ከፍተዋል።

ከሥነልቡና ድጋፍ እና የጤና ክብካቤ ጀምሮ ሙያዊ ሥልጠናዎችን የሚሰጠው ማዕከል አዳዲስ የሥራ ስምሪት መንገዶችን የሚፈጥር እና ሴቶች በማኅበረስቡ ውስጥ ለሚገባቸው ተገቢ ስፍራ ብቁ የሚያደርግ መኾኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየሴቶችን ዲጂታል የፋይናንስ ተጠቃሚነት በማሳደግ ኢኮኖሚው ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ እንዲኾኑ እየተሠራ መኾኑ ተገለጸ።
Next articleየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአቶ ክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብት አነሳ።