የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በ16ኛ መደበኛ ጉባኤው የተለያዩ ውሳኔዎችን ያሳልፋል፡፡

105

ባሕር ዳር: መጋቢት 02/2016 ዓ.ም (አሚኮ) 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 16ኛ መደበኛ ስብሰባ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

መክርቤቱ በውሎው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዕጩ ዳኞችን ሹመት፣ የፌዴራል የመንግሥት ግዥ እና ንብረት አሥተዳደር ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ የቀረበውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ እንዲሁም የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሠራተኞች አሥተዳደር ረቂቅ ደንብን በተመለከተ ያቀረበውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ እንዳለው የኢትዮጵያ የሜዳይ፣ ኒሻን እና ሽልማት ረቂቅ አዋጅን በተጨማሪም የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለዝርዝር እይታ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች እንደሚመራም ይጠበቃል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበጎጃም ኮማንድፖስት ስር የሚገኘው ክፍለጦር በሰሜን ጎጃም በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ላይ በተሟላ ሁኔታ ሕግ የማስከበር እርምጃ እየወሰደ መኾኑን አስታወቀ።
Next article“የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካን በአጭር ጊዜ ወደ ሥራ ለማስገባት በትኩረት እየተሠራ ነው” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ