የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ በመረዳት በክልሉ ያሉ ባለሃብቶች ሰላምን ለማረጋገጥ ሚናቸውን እንዲወጡ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ጥሪ አቀረቡ።

65

አዲስ አበባ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በክልሉ ከሚገኙ ባለሃብቶች ጋር በክልሉ ሰላም እና ልማት ዙሪያ ምክክር እያካሄዱ ነው።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በክልሉ ባለፉት ስምንት ወራት በነበረው ግጭት ከፍተኛ የሰብዓዊ ጉዳት እና የክልሉ ሕዝብ ሃብት የኾኑ ንብረቶች መውደማቸውን ገልጸዋል።

በዚህም የማኅበረሰቡ የረጅም ዘመናት የማንነት መገለጫ የኾኑ የጋራ ትስስር እሴቶች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

በዛሬው እለት ከባለሃብቶች ጋር የሚካሄደው ምክክር የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ በማስገንዘብ በአማራ ክልል የኢኮኖሚ እድገት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ባለሃብቶች ለክልሉ ሰላም መረጋገጥ የበኩላቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ነው ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ በመክፈቻ ንግግራቸው፡፡

ዘጋቢ፡- ቤተልሄም ሰለሞን

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ” መጽሐፍ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በአብርሆት ቤተ መጽሐፍት እየተደረገ ይገኛል፡፡
Next articleለፓን-አፍሪካዊነት ማበብ ትልቅ አበርክቶ የነበረው የኢትዮ-ጋና ግንኙነት ከፖለቲካ ባሻገር በኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ መስኮችም ሊጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡