ከኢትዮጵያ ጋር ለተፈራረመችው ሥምምነት ተፈጻሚነት ቁርጠኛ ኾና እየሠራች መኾኑን ሶማሊላንድ አስታወቀች፡፡

46

ባሕር ዳር፡ የካቲት 13/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የሶማሊላንድ መንግሥት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የተፈራረመውን የመግባቢያ ሥምምነት ዳር ለማድረስ ቁርጠኛ መኾኑን አስታውቋል።

የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ በሂ ሀገራቸው ከወር በፊት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ሥምምነት ዳር ለማድረስ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናዎኗን አስታውቀዋል፡፡

እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለጻ ሥምምነቱን ዳር የሚያደርስ ቴክኒካል ኮሚቴ ማዋቀር፣ ዓለም አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች ቡድን ማደራጀት እና ከፍተኛ የሕገ መንግሥት አማካሪ ግብረ ኀይል የማደራጀት ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቁመዋል ሲል ኢንሳይድ አፍሪካ አስነብቧል፡፡

በታዘብ አራጋው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከ4 ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶች አማራ ክልልን መጎብኘታቸውን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
Next article“የአማራ ሕዝብ ታላቆቹን የሚያከብር ታላቅ ሕዝብ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)