በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በአባላቱ የተለያዩ ጥያቄዎች እየተነሱ ይገኛል።

30

ባሕር ዳር: ጥር 28/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በአባላቱ የተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች👇

👉 በሀገራችን የሚከሰቱ አለመረጋጋቶች እና የጸጥታ ችግርች አንዱ መንስኤ የኾነውን የተዛባ እና ነጠላ ትርክት ሀገራዊ ትርክት ለመገንባት በሚሠራው ሥራ ላይ ማብራሪያ ቢሰጥበት? ከሕዝቡስ ምን ይጠበቃል?

👉 መንግሥት የልዩነት ሃሳብ ያላቸውን ኀይሎች የማሰርና የማዋከብ ጫና እያሳደረ ነው ለሚሉ ኀይሎች ምን ምላሽ አለው?

👉 ተጀምረው ያልተጠናቀቁ እና ያልተጀመሩ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ምን የተለየ የመፍትሔ አቅጣጫ ተቀምጧል?

👉 በማዳበሪያ ስርጭት ምዝበራን እና ሕገ ወጥ የማዳበሪያ ንግድን ከመከላከል እና ለአርሶአደሩ ያለ እንግልት በወቅቱ እንዲደርስ ለማድረግ ምን እየተሠራ ነው?

👉 የሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመቆጣጠር መንግሥት ምን እየሠራ ይገኛል?

👉 ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ በተፈራረመችው የወደብ የመግባቢያ ሠነድ የቀጣናው እና አንዳንድ ሀገራት የሚያስተጋቡትን ኢትዮጵያን የሚጎዳ የዲፕሎማሲ ጫና ለማርገብ ምን እየተሠራ ነው?

👉 አንዳንድ የልማት ፕሮጀክቶች ሳይጀመሩ መዘግየት እና ከተጀመሩ በኋላም የመጓተት ሁኔታን ለማረም ምን እየተሠራ ነው?

👉 በአንዳንድ ክልሎች በተከሰተው ድርቅ የዜጎች ህይወት በረሃብ እንዳይቀጠፍ መንግሥት ምን እየሠራ እንደኾነ ቢያብራሩልን።

👉 የስፖርት ጨዋታዎች ውርርድ እየተስፋፋ መምጣቱ ለተለያዩ ችግርች እንደሚዳርግ ይታወቃል። ድርጊቱ የሃገራችን ወጣት የከፋ ችግር ውስጥ ከማስገባቱ በፊት መንግሥት እንዴት ይመለከተዋል?።

👉 የሀገራችን ቱሪዝም ዘርፍ ምዕራባውያን ስለ ሰላማችን በሚያወጡት አፍራሽ መግለጫ ጫና እየተፈጠረበት ይገኛል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ የቱሪስት ቁጥር እንዲጨምር እና አዳዲስ መስህቦችን ለማስተዋወቅ ምን እየተሠራ ይገኛል?

👉 ከዲያስፖራው ማኅበረሰብ ጋር ያለውን ፖለቲካዊ ቅራኔን ለመፍታት በመንግሥት በኩል ምን ታስቧል?

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአማላይ ቃላት የሚፈጸም ሕገ ወጥ ተግባር
Next article“የሰላም ችግሮቻችን የኢትዮጵያን አንድነት እና ብሔራዊ ጥቅም ማዕከል ያደረጉ አይደሉም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)