84ኛው የአገው ፈረሰኞች ማኅበር ዓመታዊ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ አስታወቀ።

15

እንጅባራ: ጥር 23/2016 ዓ.ም (አሚኮ)የአገው ፈረሰኞች ማኅበር ዓመታዊ በዓል ”የሰላም አርበኝነት ለወንድማማችነት” በሚል መሪ ሃሳብ ለ84ኛ ጊዜ በእንጅባራ ተከብሯል። በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁንም የብሔረሰብ አሥተዳደሩ የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ገልጿል።

የመምሪያው ኀላፊ ጌታቸው ቢሻው 84ኛው የአገው ፈረሰኞች ዓመታዊ በዓል ታሪካዊ እና ባሕላዊ እሴቱን ጠብቆ በሰላም መከበሩን ተናግረዋል። በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ተሳትፎ ለነበራቸው የጸጥታ ተቋማት፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እና ለሰላም ወዳዱ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ሕዝብ ምሥጋና አቅርበዋል።

ዘጋቢ፡- ሳሙኤል አማረ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበተከናወነው የተፈጥሮ ሃብት ሥራ የደን ሽፋን መጨመሩን የደቡብ ጎንደር ዞን አስታወቀ።
Next articleትምህርት ሚኒስቴር ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ያስገነባው የጸመራ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ኾነ።