
ባሕር ዳር: ጥር 23/2016 ዓ.ም (አሚኮ) 6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ ያካሂዳል፡፡
ምክር ቤቱ በዛሬው መደበኛ ስብሰባው የ12ኛ መደበኛ ስብሰባን ቃለ ጉባዔ እንደሚያጸድቅ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ምክር ቤቱ በስብሰባው የፍትሕ ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያዳምጥና እንደሚወያይበትም ተጠቁሟል፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!