ሞሀ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ በአዲስ አሠራር ወደ ሥራ ሊገባ መኾኑን አስታወቀ።

66

አዲስ አበባ: ጥር 22/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ለአራት ወራት ሥራ አቁሞ የነበረው ሞሀ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ወደ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩብ በመቀላቀል አዲስ ሥርዓትን አዋቅሮ ወደ ሥራ ሊገባ መኾኑን የሚድሮክ የኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ኀላፊ ሰዒድ ሙሐመድ ገልጸዋል።

ኢንዱስትሪው 45ኛ የሚድሮክ የማኒፋክቸሪንግ ዘርፍ ኾኖ እንደሚሠራ ነው አቶ ሰዒድ ያብራሩት። ተቋርጦ የነበረውን ምርት በአዳዲስ የለስላሳ መጠጦች በጥራት እና በብዛት በማምረት ወደ ሕዝቡ እንዲደርስ እንደሚደረግም አስገንዝበዋል።

ኢንዱስትሪው ከፔፕሲኮ ጋር ተቀናጅቶ ሊሠራ መኾኑንም ኀላፊው ጠቅሰው ለአዳዲስ ሠራተኞች የሥራ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡

ሞሀ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪም በሀገር ውስጥ ስምንት ፋብሪካዎች ያሉት መኾኑ ተገልጿል።

ዘጋቢ፡- ራሄል ደምሰው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleትምህርት ሚኒስቴር በሰሜኑ ጦርነት ወድሞ የነበረውን የዘናልቃ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመልሶ ግንባታ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት አደረገ።
Next articleየመሬት አያያዝ ክፍተቶችን በመለየት እና በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ገለጹ።