
ባሕር ዳር: ጥር 20/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ጋር በመሆን በጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጂዮርጂያ ሜሎኒ አስተናጋጅነት በተሰናዳው የጣልያን-አፍሪካ ጉባኤ ታድመዋል።
ጉባኤው “የጋራ እድገት ድልድይ” በሚል ጭብጥ እየተካሄደ ይገኛል።
በጉባኤው ‘ማቲዬ ፕላን ፎር አፍሪካ’ የተሰፕው የጣልያን ዕቅድ ቀርቦ ውይይት እንደሚካሄድበት ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!