
ባሕር ዳር፡ ጥር 15/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በዛሬው እለት ውይይት በማድረግ ላይ ነው።
ኮሚቴው ሀገራዊ፣ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ ገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ ይሆናል።
ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ አንድምታ ያላቸው ይዘቶች በመርሀግብሩ ላይ በአግባቡ የሚመከርባቸው ሲሆን እንደ ሀገር በብሔራዊነት ትርክት የጀመርነውን ጉዞ ማጠናከር የሚችሉ ግብአቶች እንደሚገኙበት ይጠበቃል።
ውይይቱ በቀጣይ ቀናትም ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ገለፃዎች እና የቡድን ውይይቶች የመርሀ ግብሩ አካል ናቸው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!