ኢትዮ ቴሌኮም በ6 ወር የሥራ አፈጻጸም ከ42 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።

15

ባሕር ዳር: ጥር 14/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮ ቴሌኮም በ6 ወር የሥራ አፈጻጸም 42 ነጥብ 86 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱም ገልጿል። ኢትዮ ቴሌኮም የ2016 አም የበጀት አመት የመጀመሪያ መንፈቅ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርቧል።

በሪፖርቱም በ6 ወር ዉስጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን የተናገሩት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ የደንበኞች ብዛት 74 ነጥብ 6ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል ነው ያሉት።

በግማሽ ዓመቱ በተደረጉ የኔትወርክ ማስፋፊያ በ3G በ4G በ5G በአጠቃላይ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ተጨማሩ ደንበኛ የሚያሰተናግድ አቅም መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በ6 ወር የሥራ አፈጻጸም ከ42 ነጥብ 86 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱም ተገልጿል።

በራሔል ደምሰው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ባለፉት አምስት ወራት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል” የሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት
Next articleከግማሽ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር መዳበሪያ ወደ ዩኒየኖች መካዘን ገብቷል” የአማራ ክልል የኀብረት ሥራ ማኀበራት ማስፋፊያ ባለሥልጣን