“በሚቀጥሉት አስር ቀናት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት ያገኛሉ” ኢንስቲትዩቱ

18

ባሕር ዳር: ጥር 13/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በሚቀጥሉት አስር ቀናት በሰሜን ምስራቅ፣ በመካከለኛው እና የደቡብ አጋማሽ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት እንደሚያገኙ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ።

እንደ ኢንስቲትዩቱ መግለጫ በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ፣ በምስራቅ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የሚኖረው እርጥበት የበልግ እርሻ እንቅስቃሴን ቀድመው ለሚጀምሩ አካባቢዎች አስፈላጊ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ለእንስሳት የግጦሽ ሳር እና ለመጠጥ ውኃ አቅርቦት እንዲሁም ለሰብሎች እና ለቋሚ ተክሎች የውኃ ፍላጎት ለማሟላት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ገልጿል፡፡

የሚኖረው እርጥበት ለማሳ ዝግጅትና ዘር ለመዝራትም የሚጠቅም በመሆኑም አስፈላጊው እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባ አሳስቧል።

በዚሁ ወቅት የላይኛው እና መካከለኛው ስምጥ ሸለቆ፣ ኦሞ ጊቤ፣ አፋር ደናክል፣ የመካከለኛው እና ምስራቃዊ ዓባይ የላይኛው ባሮ አኮቦ፣ አዋሽ፣ ገናሌ ዳዋ እና ዋቤ ሸበሌ ተፋሰሶች መጠነኛ እርጥበት እንደሚያገኙ አስታውቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በዚህ ዓመት 310 ተፋሰሶች ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውኃ እቀባ ሥራ ለመሥራት የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተከናውኗል” የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር
Next articleኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን በድል ያጠናቀቀችበት ታሪክ የማይረሳው ቀን – ጥር 13/1954 ዓ.ም