ኬንያ በኢትዮጵያ መሪ ስም የሰየመችው መንገድ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

41

ባሕር ዳር: ጥር 13/2016 ዓ.ም (አሚኮ)የናይሮቢ የፍጥነት መንገድ በቀድሞው የኢትዮጵያ ንጉስ በአጼ ከኃይለ ሥላሴ ስም ተሰይሟል፡፡

የኬንያ መንገድ እና ትራንስፖርት ሚኒስትር ኪፕቾምባ ሙርኮመን መንገዱን መርቀው ሥራ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የፍጥነት መንገዱ ወደ ናይሮቢ ሲቲ ሴንተር መግባት የሚያስቸል መሆኑን ነው፡፡

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) እንዲመሰረት ከፍተኛ ሚና በተጫወቱት በአፄ ኃይለ ሥላሴ ስም የተሰየመው መንገድ የመጀመሪያው የናይሮቢ የፍጥነት መንገድ እቅድ አካል ነው ተብሎለታል፡፡

ላለፉት 6 ወራት በመገንባት ላይ እንደነበርም የመንገድ እና ትራንስፖርት ሚኒስትሩ መግለጻቸውን ኤንቲቪ ዘግቧል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ነባር የእርሻ እርከኖችን ማጠናከር እና አዳዲስ እርከኖችን በመሥራት የተጎሳቆሉ ቦታዎችን መጠገን ይገባል” የደቡብ ወሎ ዞን
Next article“በዚህ ዓመት 310 ተፋሰሶች ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውኃ እቀባ ሥራ ለመሥራት የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተከናውኗል” የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር