
ባሕር ዳር: ጥር 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ)2 ሺህ 16ኛው የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ታቦር ከተማ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች እየተከበረ ነው።
የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ሚካኤል በጥምቀተ ባሕሩ ለታደሙ የመንፈስ ልጆቻቸው ቡራኬ ሰጥተዋል።
ትምህርት በሊቃውንት እና ዝማሬ በካህናት ታጅቦ የጥምቀት በዓል በአጅባር ሜዳ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
መረጃው የደብረ ታቦር ከተማ ኮምዩኒኬሽን ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!