
ባሕር ዳር: ጥር 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ እንዳሉት የጥምቀት በዓል በመተሳሰብ፣ በፍቅርና በሠላም የምናከብረው፣ ከመለያየት ይልቅ በአንድነት፣ እርስ በእርስ ከመፎካከር ወጥተን በወንድማማችነት በኅብር አብረን የምንደምቅበት እንዲሁም ሃይማኖታዊ እና ባሕላዊ ይዘቱን ጠብቆ፤ በማራኪ ትዕይንቶች ታጅቦ የሚከበር ድንቅ በዓል ነው።
የንስሐና፣ የድኅነት እና ትህትና ማሳያ ለሆነው የጥምቀት በዓል እንኳን አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ በሠላም፣ በፍቅርና በአንድነት ይከበር ዘንድ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ብለዋል፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!