በወልድያ ከተማ ከ900 በላይ የሚኾኑ አረጋውያን እና አቅመ ደካሞች የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ ተጋርተዋል፡፡

17

በወልድያ ከተማ አሥተዳደር በሦስቱ ክፍለ ከተሞች ለአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል መዋያ ድጋፍ ተደርጓል።

ድጋፍ የተደረገው በከተማው በሚገኙት በእቴጌ ጣይቱ፣ በታላቁ ራስ አሊ እና በየጁ ክፍለ ከተሞች በወጣቶች እና ሴቶች አስተባበሪነት ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች እና ተቋማቶች በተሰበሰበ ሃብት ነው።

የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አለምነው ጌጡ እንደገለጹት የማዕድ ማጋራቱ የመደጋገፍ እና የመረዳዳት እሴትን የበለጠ የሚጠናክር መኾኑን ገልጸዋል። ለዚህ በጎ ተግባር መሳካት ትብብር ላደረጉ አካላቶች ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ምንጭ፡- የወልደያ ከተማ አሥተዳዳር ኮሙዩኒኬሽን

Previous articleየቅዱስ ላሊበላ የልደት በዓል በሰላም እንዲከበር ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ገለጹ፡፡
Next articleየቋሪት እና የአዴት ወረዳዎች አሥተዳደሮች እና ነዋሪዎች ለመከላከያ ሠራዊት የእርድ እንስሳት እና የገንዘብ ድጋፍ አበረከቱ።