
ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ኾነች።
ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈጽማለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) እና የሶማሊ ላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ባሂ ሁሉን አካታች የኾነውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።
በዚሁ መሠረት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ኾና የቆየችው ሀገራችን ከሶማሊ ላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት በሊዝ የወደብ ባለቤት መኾን ችላለች።