“ሀገራዊ ምክክሩ በተፈለገው ጊዜ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል” አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ

19

ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 16/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አፈፃፀም ላይ የተደረገ የመስክ ምልከታ ሪፖርት በዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ቀርቧል።

ሪፖርቱ አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሚዲያ ተቋማት መሪዎች እና የምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በተገኙበት ቀርቧል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ በዚሁ ወቅት፤ በሀገራዊ ምክክሩ ትኩረት የሚሹ ዋና ዋና ጉዳዮችን በመለየት በተፈለገው ጊዜ እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በሲዳማ፣ በሐረሪ እና በቤንሻጉል ክልሎች እንዲሁም በኮሚሽኑ ዋና መ/ቤት በመገኘት የምክክር ኮሚሽኑ ተግባር እና ሂደት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ምልከታ ማድረጉ በቀረበው ሪፖርት ተመላክቷል።

በቀረበው ሪፖርት መነሻነትም ውይይት እየተደረገ መሆኑን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የሰላም እጦት ችግሩ የዘላቂ ህልውናችን መሰረት በኾነው ጣና ሐይቅ ላይም የከፋ ፈተና ደቅኖበታል” የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ
Next article“ኢትዮጵያ ከምታመርታቸው የምርት አይነቶች 5ሺህ 700 ምርቶች በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ላይ ይሁንታ አግኝተዋል” የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር